mirage

ሂደት ተኮር የመፃፍ ትምህርት አቀራርብ የተማሪዎችን የመፃፍ ችሎታና ተነሳሽነት ለማጎልበት ያለው ሚና (በዘጠነኛ ክፍል ተተኳሪነት)

DSpace Repository

Show simple item record

dc.contributor.author ባይለየኝ, መላኩ
dc.date.accessioned 2022-03-22T08:06:08Z
dc.date.available 2022-03-22T08:06:08Z
dc.date.issued 2013-03-13
dc.identifier.uri http://hdl.handle.net/123456789/4770
dc.description.abstract የዚህ ጥናት ዓብይ አላማ ሂደት ተኮር የመፃፍ ት/ት ዓቀራረብ የተማሪዎችን የመፃፍ ችሎታና ተነሣሽነት ለማጐልበት ያለውን ሚና መመርመር ነው፡፡ ጥናቱ ከፊል ፍትነታዊ ሲሆን፣ የተካሄደው በአማራ ክልል በምስራቅ ጐጃም ዞን በሉማሜ ከተማ በሉማሜ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት የዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ከዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል በቅድመ ፈተና በተለዩ አንድ የሙከራ ቡድን እና በአንድ የቁጥጥር ቡድን ላይ ተካሂዷል፡፡ የጥናቱ ቦታ በአመቺ የናሙና ስልት የጥናቱ ተተኳሪዎች በዓላማ ተኮር የንሞና ዘዴ ተመርጧል፡፡ የልምምድ ተግባሩን የሚሰጥ አንድ መምህር በአላማ ተኮር ናሙና ዘዴ ተመርጧል የጥናቱ የመረጃ ምንጨች ቅድመና ድህረ ፈተና እንዲሆን ቅድመና ድህረ የፅሁፍ መጠይቅ ናቸው፡፡ ቅድመ ፈተናው የተሰጠበት አላማ ተማሪዎች ከሙከራ ጥናቱ በፊት ያላቸውን የመጻፍ ውጤት ተቀራራቢ መሆን/ አለመሆኑን ለመፈተሸ ሲባል ነው፡፡ የድህረ ፈተናው አላማ ደግሞ የሙከራና የቁጥጥር ቡድን ሆነው የተመረጡት ተማሪዎች በተለያዩ የማስተማሪያ ዘዴዎች የመጻፍ ክሂልን ከተማሩ በኃላ በመካከላቸው ጉልህ ልዩነት መኖር/ አለመኖሩን ለማረጋገጥ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ቅድመ የፅሁፍ መጠይቅ እንዲሞሉ የተደረገበት አላማ ተማሪዎች ከሙከራ ጥናቱ በፊት ያላቸውን የመፃፍ ተነሣሽነት ተቀራራቢ መሆን አለመሆኑን ለመፈተሽ ነው፡፡ ድህረ የፅሁፍ መጠይቅ እንዎች የመፃፍ ክሂልን ከተማሩ በኋላ በመካከላቸው ጉልህ ልዩነት መኖር አለለመኖሩን ለማረጋገጥ ነው፡፡ በቅድመ ፈተናና የፅሁፍ መጠይቅ እንዲሁም በድህረ ፈተናና የፅሁፍ መጠይቅ የተገኘው ውጤት በነፃ ናሙና ቲ -ቴስት እንዲሰላ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም በቅድመና በድህረ ፈተና፣ በቅድመና በድህረ የፅሁፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድ ናሙና ቲ -ቴስት ቀመር እንዲሰላ ተደርጓል፡፡ en_US
dc.description.sponsorship uog en_US
dc.language.iso en_US en_US
dc.publisher uog en_US
dc.subject በተጨማሪም በቅድመና በድህረ ፈተና፣ በቅድመና በድህረ የፅሁፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድ ናሙና ቲ -ቴስት ቀመር እንዲሰላ ተደርጓል፡፡ en_US
dc.title ሂደት ተኮር የመፃፍ ትምህርት አቀራርብ የተማሪዎችን የመፃፍ ችሎታና ተነሳሽነት ለማጎልበት ያለው ሚና (በዘጠነኛ ክፍል ተተኳሪነት) en_US
dc.type Thesis en_US


Files in this item

This item appears in the following Collection(s)

Show simple item record

Search in the Repository


Advanced Search

Browse

My Account