Abstract:
የዚህ ጥናት ዋነኛ ዓላማ ስነ-ፅሁፋዊ ውይይት የተማሪዎችን አንብቦ የመረዳት ችሎታና ማህበራዊ
ክህሎት በማሳደግ ረገድ የሚኖረውን ሚና በከፊል ሙከራዊ ጥናት (quasi experimental design)
አማካይነት መፈተሸ ነው፡፡ የጥናቱ ተተኳሪዎች በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ
በሚገኘው የአይከል መሰናዶና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚማሩ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ሲሆኑ
ጥናቱ የተካሄደበት ትምህርት ቤት የተመረጠው አጥኝዋ የምታስተምርበት ትምህርት ቤት በመሆኑ
ባለው አመቺነት የተነሳ ነው፡፡ ይህ ከፊል ሙከራዊ ጥናት የሁለት ቡድን ቅድመና ድህረ ትግበራ ፈተና
ንድፍ ስለሚከተል በዚሁ ትምህርት ቤት አራት የ11ኛ ክፍል ምድቦች መካከል የ11ኛ B ተማሪዎች
በቁጥጥር ቡድን የ11ኛ C ክፍል ተማሪዎች ደግሞ በሙከራ ቡድን ታቅፈው የጥናቱ ተሳታፊዎች
እንዲሆኑ ቅድመ ትግበራ አንብቦ የመረዳት ፈተናና የማህበራዊ ክህሎት መጠይቅ ከወሰዱ በኋላ በዕጣ
ተደልድለዋል፡፡ በሁለቱም ቡድኖች ያሉ ተማሪዎች አጠቃላይ ብዛት 96 ሲሆን እያንዳንዳቸው 48
ተማሪዎችን ይዘዋል፡፡ ከፊል ሙከራዊ ጥናቱ በተከናወነባቸው የስድስት ሳምንት ጊዚያት የሙከራ
ቡድኑ በ11ኛ ክፍል የቀድሞ ስርዓተ ትምህርት ውስጥ የቀረቡ የንባብ ትምህርት ይዘቶች በስነ-ፅሁፋዊ
ውይይት አማካይነት እንዲማር ሲደረግ የቁጥጥር ቡድኑ አባላት ደግሞ በተለምዷዊው ተማሪ ተኮር
ዘዴ አማካይነት እንዲማሩ ተደርጓል፡፡ የመማር ማስተማር ሂደቱ የተደረገው በተቃራኒ ፈረቃ ነው፡፡
ለዚህ ጥናት የሚሆኑ መረጃዎች የተሰበሰቡት በፈተናና የማህበራዊ ክህሎት መጠይቅ አማካይነት ነው፡፡
በእነዚህ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች የተሰበሰበው መረጃ