mirage

በሶስተኛና አራተኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጻህፍት የስርዓተጾታ ፍትሃዊነት ፍተሻ

DSpace Repository

Show simple item record

dc.contributor.author ሺባባው ሞላ1, አራጋው
dc.date.accessioned 2019-01-10T07:25:15Z
dc.date.available 2019-01-10T07:25:15Z
dc.date.issued 2018-07-05
dc.identifier.uri http://hdl.handle.net/123456789/1904
dc.description.abstract ይህ ጥናት በሶስተኛና በአራተኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጻህፍት የስርዓተጾታ ፍትሃዊነት ምን እንደሚመስሉ መመርመር ላይ ያተኮረ ነው። ለዚህም ሁለቱ መማሪያ መጻህፍት በዓላማ ተኮር ስልት ተመርጠዋል። መረጃዎችም በሰነድ ፍተሻ ስልት ተሰብስበዋል። የተሰበሰቡ መረጃዎም በካይ ካሬ፣ በድግግሞሽ ቆጠራ፣በሬሾና በመቶኛ ተተንትነዋል። ከተገኘው ትንተና እንደተስተዋለውም፣ ሴቶች በስም የቀረቡበት የድግግሞሽ መጠን 66(54.09%) ሲሆን ወንዶች የቀረቡበት የድግግሞሽ መጠን ደግሞ 56(45.9%) ነው። የካይ ካሬ ፍተሻ እንዳሳየውም p>0.05 ሆኗል። የጉልህነት ውጤቱም .157 ሆኗል። ይህም በሁለቱ ጾታዎች መካከል የጎላ ልዩነት እንደሌለ የሚያሳይ ነው። የሴት ወንድ የስም ድግግሞሽ ሬሾ/ጥምርታ/ ሲታይ ደግሞ 1.12 ሴት ለ1 ወንድ ነው፡፡ ከዚህ አንጻርም በጾታ ድግግሞሽ የጎላ ልዩነት አልተስተዋለበትም። የሁለቱ ጾታዎች ማህበራዊ ሚና ሲታይ መጻህፍቱ ሴቶች ዋናዋና በሚባል ደረጃ በብዛት የቀረቡበት ሚና የለም። ከተሳተፉባቸው ሚናዎች መካከል ግን ሴቶችን መግረዝ፣ ዳቦ መግዛት፣ ዳቦ መሸጥ፣ ልጅ መንከባከብ፣ የህክምና ምክር መስጠት፣ መብት መጠየቅ፣ በሽተኛ መንከባከብ ይገኙበታል። ኳስ መጫዎት፣ በሽተኛ ተሸካሚ መሆን፣ ሩጫ ደጋፊ መሆን፣ ሳርቤት መክደን፣ፖሊስና ሹፌር ሆኖ መስራት ወንዶች በብዛት የተሳተፉባቸው ዋናዋና ሚናዎች ናቸው። ከዚህ አንጻር ሚና ላይ የፍትሃዊነት ችግር አለ ማለት ይቻላል፡፡ ውክልናን በተመለከተ ደግሞ በሁለቱም ጾታዎች ሴት ወይም ወንድ ሲባል ትዝ በሚል መንገድ የተስተዋሉ ውክልናዎች የሉም ማለት ይቻላል፡፡ ሳይደጋገሙ የቀረቡ ውክልናዎች ሲታዩ ግን ወንዶች በአንጻራዊነት በተሻሉ ነገሮች የተወከሉ ሲሆን ሴቶች ደግሞ ዝቅ ባሉ ነገሮች ተወክለው ቀርበዋል። ይህም ከውክልና አንጻር ክፍተት መኖሩን የሚያሳይ ነው። በመሆኑም ወደፊት የስርዓተትምህርት አዘጋጆች በሚያዘጋጇቸው መጻህፍት ጥንካሬዎቹን በማስቀጠል በድክመቶቹ በኩል ማሻሻያ ቢያደርጉ መልካም ነው። en_US
dc.language.iso en en_US
dc.subject መማሪያ መጽሃፍ፣ ስርዓተ-ጾታ፣ ሚና፣ ውክልና en_US
dc.title በሶስተኛና አራተኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጻህፍት የስርዓተጾታ ፍትሃዊነት ፍተሻ en_US
dc.type Article en_US


Files in this item

This item appears in the following Collection(s)

Show simple item record

Search in the Repository


Advanced Search

Browse

My Account